news

Previous Next

 

የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓትን መተግበር የጊዜና ጉልበት ብክነት ከማስቀረቱ ባሻገር ግልጸኝነትና ተጠያቂነትን በማስፈን በህዝብና መንግስት መካከል መተማመን የሚያጎለብት መሆኑንም በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ አስታውቋል።
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ እና ፔራጎ እንፎርሜሺን ኋ.የተ.የግ.ማ. ከሚባል ሶፋትዌር ድርጅት መካከል የተመረጡ መንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ኢ.ጂ. ፒ. (eGP) ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድርግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ።
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አራርሶ ገረመው ከጨረታ ሂደት ጋር በተያያዘ የወረቀት ንኪክና የጊዜና የጉልበት እንዲሁም አለአግባብ የሚወጡ የተለያዩ ወጪዎችን ማስቀረት መቻሉን ጠቁመው፤ በከፍተኛ ሁኔታ የመንግስት ሀብት ከብክነት ማዳን መቻሉን በአስተያየታቸው አብራርተው የዛሬው ሥምምነት ለክልላችን ታሪካዊ ሥምምነት መሆኑን ገልፀው ወደዚህ መተግበሪያ ተጠቃሚነት ውስጥ የሚገቡ ቢሮዎችና ከተማ አስተዳደሮች ለህዝባቸው ባለውለታ ናቸው ብለዋል ።
ኃላፊው አክሎም በሲዳማ ብሔራዊ ክልል ፋይናንስ በሥሩ ያሉ 50 የሚደርሱ ቀጥታ online ሥራ መጀመሩን ጨምረው ገልፀው በቀጣይም የchek አልባ ፋይናንስ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ እንዳሉት ባለስልጣኑ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓትን መተግበር ግልጽነትና ተጠያቂነትን በማስፈንና ብልሹ አሠራርን በማስወገድ በመንግስትና በህዝብ መካከል መተማመን እንዲኖር ያደርጋል" ብለዋል። አክሎም የሲዳማ ክልላዊ መንግስት ይህን መተግበሪያ ተቀብለው ከሁሉም ክልሎች ቀዳሚ በመሆን ተግባራዊ በማድረጋቸው የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ሀሳባችን ተቀብሎ ወደ ሥራ እንድንገባ ሌተቀን ድጋፍ ማድረጋቸውን አመስግነዋል።
የፋይናንስ ቢሮ ህዝብ ግኑኝነት ዳይረክቶሬት
ቀን ህዳር 3/3/2016 ዓ.ም
ሀዋሳ

About Us

የሲዳማ ህዝብ፡ ከ100 ዓመታት የፓሌቲካ ትግል በኃላ፣ የቀደመ የመንግሥት፡ አስተዳደሩን በመመለስ እነሆ በዚህ በለውጥ ዘመን የለውጥ ዕይታ ይዞ፡ ሀገራችንንም፡ በተገባላት፡ ቃል ኪዳን መሠረት ፡ ዐለቷ እንዲ ፀና እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ዋጋው፡ ከፍ ያለ ነው፡፡ የኢትዮጱያ ድምቀት በመሆናችን እንኳን ደስ አለን!!

Flickr Photos

Address

address: Beside of Hawassa City Primary Court

phone (+251) 13181046

Email : snrsbof@snrsfb.gov.et

Fax(046)-220-60-84        

PostP.S.K. 485

Usefull Links

Announcement

Bid

Vacancy

Contact

 

Social Media

FaceBook

Youtube

Google Map

     WhatsApp

     Telegram